Testo Addis Ababa - Fikeraddis Nekatibeb
Testo della canzone Addis Ababa (Fikeraddis Nekatibeb), tratta dall'album Misikir
ሳናዎጋ ነጋ ነጋ ነጋ
ሃገሬ ወይና ደጋ: ወይና ደጋ
ሳናዎጋ: ነጋ ነጋ ነጋ
ሃገሬ ወይና ደጋ: ወይና ደጋ
ወይና ደጋ: ወይና ደጋ: ሳላዎጋ ነጋ
ወይና ደጋ: ወይና ደጋ: ሳላዎጋ ነጋ
እያለ ነጋ: እያለ ነጋ
ሆሆሆሆ ሃገሬ ወይና ደጋ
እያለ ነጋ: እያለ ነጋ
ዬዬዬሄሄሄ ሃገሬ ወይና ደጋ
አዲስ አበባ ላይ (የኔ የኔ) ተነገረ አዋጅ (የኔ የኔ)
ላንተ መሳይ ቆንጆ (የኔ የኔ) ላኔ መሳይ ልጅ (የኔ የኔ)
ሰረገላ እንዲጫን (የኔ የኔ) ሰልፍ እንዲዘጋጅ (የኔ የኔ)
እንዲተከል ድንኳን (የኔ የኔ) ለእንግዳ ወዳጅ (የኔ የኔ)
ግብር አስርቶ: ይጠብቃል እንጅ
ቃል አያጓድልም: ያአዲሳባ ልጅ
የሸገር አይናማ: አንተ የኔ ተቀባይ
በል ጠብቀኝ እንጅ: ጃንሜዳ አደባባይ
ኮኮብህ ኮኮቤ: የገጠመ ለታ: የገጠመ ለታ
ውድህና ውዴ: የገጠመ ለታ: የገጠመ ለታ
ለማሪያም መቀነት: ለገብርዔል ኩታ
ይህንን አድርጌ: እኔ ወዳጅህ
የምነግርህ አለኝ: የማጫውትህ
አጫውትሃለሁ: ወግ አሰባስቤ
ቁመቴም እንኳን ቢያጥር: ረዥም ነው ልቤ
ቁመቴም እንኳን ቢያጥር: ረዥም ነው ልቤ
አሆ ኦሆ የኔ አለም (የኔ የኔ)
አሆ ኦሆ የኔ አለም (የኔ የኔ)
አሆ ኦሆ የኔ አለም (የኔ የኔ)
ከዘር ከሃይማኖት (የኔ የኔ) ከቋንቋም ከነገድ (የኔ የኔ)
ሸገር ላይ ይተማል (የኔ የኔ) በአራት መንታ መንገድ (የኔ የኔ)
አቤት አፈጣጠን (የኔ የኔ) አዲስ ሰው ለማልመድ (የኔ የኔ)
ከዚህ ይመነጫል (የኔ የኔ) የኔና አንተ መውደድ (የኔ የኔ)
በአራቱም ማዕዘን: አውጥቶ እያገባ
ስንቱን አዋደደ: ወይ አዲስ አበባ
እንያያዝና: በል እንዘናከት
የፍቅር አባዜ: ወይ አለመታከት
ኮኮብህ ኮኮቤ: የገጠመ ለታ: የገጠመ ለታ
ውድህና ውዴ: የገጠመ ለታ: የገጠመ ለታ
ለማሪያም መቀነት: ለገብርዔል ኩታ
ይህንን አድርጌ: እኔ ወዳጅህ
የምነግርህ አለኝ: የማጫውትህ
አጫውትሃለሁ: ወግ አሰባስቤ
ቁመቴም እንኳን ቢያጥር: ረዥም ነው ልቤ
ቁመቴም እንኳን ቢያጥር: ረዥም ነው ልቤ
አሆ ኦሆ የኔ አለም (የኔ የኔ)
አሆ ኦሆ የኔ አለም (የኔ የኔ)
አሆ ኦሆ የኔ አለም (የኔ የኔ)
አሆ ኦሆ የኔ አለም (የኔ የኔ)
አሆ ኦሆ የኔ አለም (የኔ የኔ)
አሆ ኦሆ የኔ አለም (የኔ የኔ)
አሆ ኦሆ ናናሃሃሃ የአዲሳባው
አጫውትሃለሁ: አጫውትሃለሁ: ወግ አሰባስቤ
ቁመቴም እንኳን ቢያጥር: ረዥም ነው ልቤ
ቁመቴም እንኳን ቢያጥር: ረዥም ነው ልቤ
አጫውትሃለሁ: አጫውትሃለሁ: ወግ አሰባስቤ
ቁመቴም እንኳን ቢያጥር: ረዥም ነው ልቤ
ቁመቴም እንኳን ቢያጥር: ረዥም ነው ልቤ
አሆ ኦሆ ናናሃሃሃ የአዲሳባ
Credits
Writer(s): Elias Woldemariam, Tesfa Birhan
Lyrics powered by www.musixmatch.com
Link
Disclaimer:
i testi sono forniti da Musixmatch.
Per richieste di variazioni o rimozioni è possibile contattare
direttamente Musixmatch nel caso tu sia
un artista o
un publisher.