በቃላት ድርድር በሙዚቃ ቃና
ስሜን ስታብራራ ነፍሴን ስታጣራ
አየሁኝ ጥበብ ሰማሁኝ ዕውቀት
ልናገር ልመስክር የዚህን ሰው ጽናት
ቀልጦ እንደሚበራ ሻማ
መብራት በሌለው ከተማ
እየቀለጠ በራልኝ
እየሞተ አኖረኝ
ለሱስ ባለእዳው ነኝ
ህይወት እንዳይሰለቸኝ
ሲጨነቅ ሲጠበብ
አይተኛም ቀን ከሌት
ለደስታዬ ሲዋትት
ካህንዬ የነፍሴ አገልጋይ
እንቅልፍ አትተኛም ወይ
የነፍሴ አገልጋይ
እንቅልፍ አትተኛም ወይ
ካህንዬ የነብሴ አገልጋይ
እንቅልፍ አትተኛም ወይ
የነፍሴ አገልጋይ
እንቅልፍ አትተኛም ወይ
መሰንቆዉን ይዞ ከደጄ
ሲጫወት ያድራል ሲያዜም
በበገና በክራር ነፍሴን ሲያለመልም
እንደ መልከጼዴቅ ካህን
ክህነቱ ከዘመን ዘመን
የዘላለም አይደለም ወይ
የሰጠኝ ደስታ ከላይ
ስወድ ስጠላ የማይተወኝ
ለትንሽ ደስታው አመስጋኝ
አንዲህ ያለ ሰው የሰው ምርጥ
በጊዜ የማይለወጥ
ካህንዬ የነፍሴ አገልጋይ
እንቅልፍ አትተኛም ወይ
የነፍሴ አገልጋይ
እንቅልፍ አትተኛም ወይ
ቃል ከአንደበቱ እንደውሃ
ይፈሳል እንደ ጅረት
ልብን የሚመረምር
ጠልቆ የሚገባ ከአንጀት
ሰምና ወርቁን ተናገር
ቅኔ በለሱን ደርድር
በጻድቅ ሰው ቃላት
ነፍሴ ገባች ከገነት
ጣዕሙን ዜማ ስታዜም
ቃልን ከህይወት ስትቀምም
ስጋዬን ለየህ ከነፍሴ
አቆራረጥከኝ ከእስትንፋሴ
ካህንዬ የነፍሴ አገልጋይ
እንቅልፍ አትተኛም ወይ
የነፍሴ አገልጋይ
እንቅልፍ አትተኛም ወይ
እንደ መልከጼዴቅ ካህን
ክህነቱ ከዘመን ዘመን
የዘላለም አይደለም ወይ
የሰጠኝ ደስታ ከላይ
ከላይ ከላይ
ከላይ ከሰማይ
ከላይ ከላይ
ከላይ ከሰማይ
ከሰማይ
Credits
Writer(s): Ejigayehu Shibabaw
Lyrics powered by www.musixmatch.com
Link
Disclaimer:
i testi sono forniti da Musixmatch.
Per richieste di variazioni o rimozioni è possibile contattare
direttamente Musixmatch nel caso tu sia
un artista o
un publisher.